Problems?: Download fonts      PDF

የየሱስ ክርስቶስ መንገድ

የሱስ ክርስቶስ

የየሱስ ክርስቶስ መንገድ፣ እርሱም ለሰብአዊ ፍጡር ልቦና፣ የሰውን ዘርና ምድሪቱን ለመለወጥ የሚያደርጋቸው አስተዋፅዖዎች፤ በበርካታ ምርምርና ልምድ ላይ የተመሠረቱ አዳዲስ አመለካከቶችን በማፍለቅ የግል ባህርይን ዕድገት ለማጎልበት ተግባራዊ የሆነ ጥቆማን የሚሰጥ ገለልተኛ የሆነ የመረጃ ምንጭ ነው።

በዚህ በአማርኛ ቋንቋ በተጻፈው ገፅ ከፀሎት ጋር ለተያያዙት ጉዳዮች መሠረታዊ የሆኑ ጥቆማዎችን ያገኛሉ።

  ሃይማኖት - ከየሱስ ክርስቶስ ጋር ስጓዙ - ሰዉን ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ማገናኛ ድልድይ 1)

መረጃ፦ የሱስና እስልምና 1)

 በአንዳንድ ቋንቋዎች 2) ደግሞ በአጠቃላይ ከወንጌሎችና ከዮሐንስ ራዕይ ጋር አጠቃላይ የሆኑ ሐተታዎችን የያዙ በሌሎች ብዙ ዐርዕስቶች ላይ የተጻፉትን ጽሑፎች ያገኛሉ3)

 

 1) አጫጭር ትርጉሞች፡ 

2) አጠቃላይ ትርጉሞች እንግሊዘኛ እና ጀርመንኛ ዘወትር ይሻሻላሉ ,  ፈረንሳይኛ (français) ፈረንሳይኛ ደግሞ፦

    

http://www.ways-of-christ.com/am

ለሰላም ለሕይወትና ለምድር የሚጸለይ ፀሎት

ይህ ፀሎት ደግሞ ውጤታማ ወደ ሆነው ፀሎት ሊመራ የሚችለውን፣ የክርስቲያንን አመለካከት "ያንፀባርቃል።"

እግዚአብሔር፣ መነሻዬ፣ ረድኤቴና ተስፋዬ! ከየሱስ ክርስቶስ ጋር በአንድነት ከአንተ ዝንድ ለምመጣልኝ ለሁሉም ነገር ይድረስህ ምሥጋናዬ እኔና ከአንተ አርቆኝ ለወሰደኝ ለሁሉም ነገር ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ በዚህ በዝምታ፣ እባክህን በመንፈስህ ጠቢብ አድርገኝ

ወደ አንተ የሚሄዱትን፣ ሌሎችን እንዳላሰናክል አንተ ምራኝ እንደ ፈቃድህ ሌሎችን እንድረዳ ዘንድ አንተ ምራኝ በመንገዴ አንተ አድነኝ*

ሰዎች ሞትንና ሕይወትን የተመለከቱበትን ዉሳኔዎች በአንተ እጅ ይጥሉ ዘንድ በመንፈስህ አነሳሳቸው** ለተፈጥሮህ የሚሠሩትንም እርዳቸው*** ይህን ዓለም ተስፋ ወደሰጠሃው ወደ አዲሱ ዘመን ዘልቆ ይገባ ዘንድ ምራው****

*) እዚህ ጋ ሌሎችም ሊጨመሩ ይችላሉ። **) እዚህ ጋ ዝርዝሮችም ሊጨመሩ ይችላሉ፤ ወይም ‘ሁከትን መካብ ማቆም’፣ ችግሮችን በማቃለል አንድ የሁከት መንስኤ ማስወገድ’፤ ‘ሰላማዊ ሰዎች ሰብአዊ መብታቸው ተከብሮ ለመኖር የሚያስችላቸውን የደህንነት እርምጃችን ብቻ ተግባራዊ ማድረግ’፤ ’ታዋቂ ከሆኑ ከተለያዩ የሃይማኖት ሰዎች ጋር ውይይት ለመጀመር ‘፣ ከመሳሰለው ፀሎት በኋላ በአማላጅነት ሊገባ ይችላል….በማቴዎስ 5፡ 9 ና 26፡ 52 ያለውን ማየት ይችላሉ።

***)ተፈጥሮ ለርዳታ እሪ ትላለች።ጊዜው የፅሎት ነው፡ ጌታ ሆይ ‘ክተነሳሳብን’ የተፈጥሮ ኃይል አድነን። ዳሩ ግን ይህ ከሌላው ተፈጥሮ ጋር ካለው ግንኙነት አኳያ የሰውን የባህርይ ለውጥ አይተካም።

****) ሉቃስ 11፡2፤ 21፡31። ራዕይ 11፡ 16፤… ለመፀለይ በአንድ"መንፈስ" በመሆን በአንድነት ለመኖርና ተግባራችንን ለማከናወን እንችል ዘንድ እግዚአብሔር በሁሉም ቤተ ክርስቲያናት ለርሱ የተሰጠውን ፍቅር ያከፋፍላል።

 

3) እዚህ የተጠቀሰው ዋና ጽሑፍ በሌሎች ቋንቋዎች የሚከተሉትን ምዕራፎች ይይዛል፦-ክፍል 1- የአማላጅነትን ፀሎት ጨምሮ በሥርዓት የተዘጋጁት ጥቆማዎችና የዚህ ጽሑፍ ዓላማና ጠቃሜታ መግቢያ "መጀመሪያ ቃል (በግሪክ ሎጎስ) ነበረ… እናም ቃሉም ሥጋ ሆነ"፤ የናዝሬቱ የሱስ፤ ልደቱ፤ የክርስቲያን ዳግመኞ ልደትን በተመለከተ ተጨማረ ገፅ፤ በየሱስ የወጣትነት ዕድሜ ወቅት የሚገኝ ጠቃሚ ነገር አለ ወይ ? ፤ "የሱስ ተብለው በሚጠሩ በሁለት ልጆች" መካከል የተከሰተ ጥላቻን በተመለከተ የቀረበ አስተያየት፤ በመጥመቁ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ የተከናወነ ጥምቀት፤ የዛሬውን ጥምቀት በተመለከተ ከተጨማሪ ማብራሪያ ጋር ይቀረበ ተጨማሪ ገፅ፤ በበረኃ ውስጥ ፀጥታ፤ ፈተናዎች፤ በቃና ዘገሊላ የተደረገ ሠርግ፤ (ወሲብ፣ የሌላውን ስሜት መካፈል፣ ማፅናናትንና ፍቅርን በተመለከተ የቀረበ አመለካከት)፤ "ቅዱስ ቅንአት" (ስሜቶችን በተመለከተ የቀረቡ አመለካከቶች)፤ የተራራው ላይ ስብከትና አእምሮን በተመለከተ የቀረቡ አመለካከቶች፤ በታቦር ተራራ ላይ የክርስቶስ መልክ መቀየር፤ አልአዛርን ከሞት በማስነሳቱ "ታአምራት" ላይ የቀረቡ ጥያቄዎች፤ "በጎች"፤ የክርስቶስ "የእግር እጥበት" እናም የቢታንያው ማርያም የሱስን መቀባት (ለክርስቲያን መንፈሳዊነት ጠቃሚ ነጥብ)፤ የመጨራሻው እራት፤ በድል መግባትና ግርፋት፣ የእሾህ አክሊል መደፋት" ና የመጨረሻው ንግግሮች፣ ስቅለቱና ቀብር (ከክርስትና ሃይማኖት ከቀረበ አስተያየት ጋር)፣ የባዶ መቃብር፣ ወደ "ሥዖል መውረድ" ና ወደ "ገነት እርገት" ጥያቄ፣ ትንሣኤ፣ "የክርስቶስ እርገት"፤ ጴንጤቆስጤ፣ የየሱስን ገፅታ በተመለከተ የቀረበ ጥቆማ። ክፍል 2፦ የቅዱስ ዮሐንስ ራዕይ፣ ትንቢቶች እንዴት እንደሚመረመሩ፣ የዮሐንስ ራዕይ ማውጫ፣ ሰባቱ ቤተክርስቲያናት፣ የዛሬ ቤተክርስቲያናት ልዩነታቸውንና አንድ ለመሆን ያላቸውን መንገድ በተመለከተ የቀረበ ተጨማሪ ገፅ፣ "ሰባቱ ማህተሞች"፤ "ሰባቱ መለከቶች"፤ "ሰባቱ ነጎድጓች" ና ሁለቱ ነቢያት፣ ሴቲቱና ዘንዶው፣ ከባህር ውስጥ የሚወጣ "ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ"፣ ከምደር ላይ የሚወጣ "አሥር ቀንዶች ያሉት አውሬ"፣ "ሰባቱ የቁጣ ጽዋዎች" ና የ "ባቢሎን" መጨረሻ፤ የክርስቶስ ደግመኛ መምጫ፤ (ትክክለኛው) "የሺህ ዓመት ሰላም"፤ አዲስ ሰማይ፣ አዲስ ምድርና "አዲስቷ ኢየሩሳሌም"፤ የመጨረሻ ምዕራፍ ፦ የክርስቲያን አመለካከት፣ ሠንጠረዥ፤ በዓለም እየሆኑ ከዓለም አለመሆን፣የክርስቲያኑ አመለካከት። 3፡ ሌሎች ዐርዕስቶች፦ ፀሎት፣ የሥነ ምግባር ዋጋዎች መሠረተ ሃሳብ፤ ዘመናዊ የየሱስ ማለምት ማስተካከያ፤ የሱስ፣ የሰው ምግብና እንስሣትን መጠበቅ፣ ሳይንሶችና በእግዚአብሔር ማመን፣ የሱስና ፈውስ - ዛሬም ቢሆን፣ በረከቶች፣ ክርስቲያን ለምጣኔ ሃብትና ለማህበራዊ ጥያቄዎች ያለው አመለካከት፣ ክርስቲያን ለማሀበረሰብና ለፖለቲካ ያለው አመለካከት፣ ሃይማኖትና ፍልስፍና፣ በሃቤርማስ ንግግር ላይ የተሰጠ አስተያየት፤ ያልተወለደ ፍጡር፤ እነዚህ ገጾችና ትምህርት የተለያዩ የክርስቲያን ስነ መለኮት አመለካከቶች፤ የክርስቲያን ተማህፅኖ፣ ማነቃቂያና ቤተ ክርስቲያናት፣ ከሞት በኅላ ስላለው ሕይወት ስላለው ጥያቄና ከሞት በፊት ባለው ሕይወት ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ስላለው ያለው አመለካከት፤ ክርስቲያንነት - ሌሎች ስለ "ዕድል" እና "እንደገና መፈጠር"ን በተመለከተ ከሚያስተምሩት ከሌሎች ትምህርቶች ጋር ያለው ግኑኝነት፣ 4. ብሉ ኪዳንና እርሱ ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር ለመወያየት የሚያበረከተው አስተዋፅዖ፦ ብሉይ ኪዳን፣ የአይሁድ ኃይማኖትና የሱስ፤ "የሱስና እስላም"፣ የዛራታስትራ (ፓርሥስም) ሃይማኖት፤ "ቡዳዊነት" ፣ "ሂንዱአዊነት"፣ "ታኦዝምነት"፣ኮንፍስካዝምነት"፣ ሽንቶዝምነትና የተፈጥሮ ኃይማኖቶች፣ ሃይማኖት ሰውን እንደገና ከእግዚአብሔር ጋር "የማገነኛ ድልድይ" ።

የባለቤትነት መብት፡ በዚህ ገፅ ያሉትን ጽሑፎች፡ ያለምንም ለውጥ፡ አትመው ልወሰዱ ወይም ለወዳጆች ሊያቃብሉ ይችላሉ!

ኢ ሜይል፡ እባክዎን በእንግሊዘኛ ወይም በጀርመንኛ


መጽሐፍ ቅዱስ

 

ሃይማኖት1) - ከየሱስ ክርስቶስ ጋር ስጓዙ - ሰዉን ከእግዚአብሔር ጋር እንደ "ማገናኛ ድልድይ"

 1) ሃይማኖት የሚለው ቃል መነሻው በላቲን ሪ-ሊጊዮ ሲሆን ትርጉሙም ከዉስጣችን ሆኖ በኛው ዉስጥ መልክ ከምይዘው ከእግዚአብሔር ጋር-እንደገና መገናኘት ማለት ነው። ይህም እንደ ሆሎግራም (በፎቶግራፍ ጥበብና በጨረር አማካይነት ሶስት ዓይነት ቅርፅ ያለው ፎቶግራፍ) በሰፊው ይከሰታል።

በሰብአዊ ፍጡር ሕይወት ውስጥ ያሉትን ጥልቅ ችግሮችን ማወቅ

ሰውነትን ከማዳን ባሻገር ላሉት ለውጦች ደግሞ የየሱስ የመጀመሪው ጥያቄ፡ "ልትድን ትወዳለህን?" (ዮሐንስ 5፡ 6) ነው፤ ወይም ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ ከፈለጉ፣አሁንም መለወጥ ያለብዎትን ጉድለቶች ያውቃሉ? አንድ ሰው ከቀላሉ የሕይወት ጉዳዮች በስተጀርባ ዘወትር ከሃይማኖት ጋር ግኑኝነት የሌላቸውን ማዕከላዊ የመገናኛ ክሮችን ሊያገኝ ይችላል። ጎልማሳ ለመሆን እያደገ ያለው ልጅ አዳዲስ ችሎታዎቸን ያዳብራል። ዳሩ ግን፣ ነገሮችን በፅናት ለመለማመድ የሚያስችሉት አንዳንድ የመጀመሪያዎቹ ችሎታዎች ይሰወራሉ። በኋላም አንድ ሰው እነዚህን የተፈጥሮ ችሎታዎች ለማደስ ይሞክራል። በዚህ ሁኔታ የሰው ደንዳናነት እየላላ ወይም እየጠፋ ሲሄድ፤ ተጨማሪ ችሎታዎች ግን ይቀራሉ። በአንጎልና በሕይወት መካከል ያሉት ክፍተቶች(ስብረቶች) - በ"ልብ" ውስጥ ባለው ደካማ ድልድይ፣ በአእምሮና በተፈጥሮ ሕይወት መካከል ወዳለው ክፍተት እያመሩ፣ እንደገና በተሻለ ሁኔታ ይቀናጃሉ። ይህ ክፍተት በጥንታዊው የገነቱ ታሪክ ውስጥ "መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ ስለመብላት" አንድ ትርጉም እንደሆነ ማሳየት ይቻላል። እናም "ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።" ያለው የየሱስ አባባል የተመሰረተው መመለስና መለወጥ በሚቻልበት ጥልቅ እውቀት ላይ የተመስረተ ነው(ማቴዎስ 18፡1-3፤ ማርቆስ 10፡15፤ሉቃስ 18፡17)። ይህም ሀፍረት እንደማይሰማችው ልጆች አዃኻን ዓይነት ብቻ ሳይሆን "ምሳሌያዊ" 2) ዋና የእድገት መሰረተ ሃሳብ ንድፎችን በተመለከት ነው ("ለሰው ጥቕም ትምህርት የሚሆን" የጠፋው ክፍል ማለት ነው)። ይህ መንገድ ከዛሬው ውስን የአእምሮ ንቃተ ሕሊና ባሻገር ይዘለቃል።

2) "ምሳሌያዊ" የ ሲ ጂ ጃንግና የሌሎቹ ጥልቅ የስነ አእምሮ ቃል ፤ የሰው ዘር የመኖር ገፅታዎች በተለያዩ መልኮችና ቅርፆች ለምሳሌ በሕልም ይገለጻል።  ዳሩ ግን ፣ " ዋና ተምሳሌያቱ " ደግሞ በከፍተኛ ደረጃ የተቀላቀለና አሳሳች ይዘት አለው። "እግዚአብሄር"ን እንደ ሽማግሌ አድርገው ያዩታል፣ እና " ሰማይ" ን እና "ገሃነም" ን "የማህበራዊ ህሊና " ተምሳሌያት አድርገው ይጠቅሱአቸዋል። ጃንግ ይህ በትክክል ምን እንደነበረ አላወቀም። ቢያንስ የዚህ የህሊና ደረጃ ማዕከል በተወሰነ ደረጃ በሁሉም ሰዎች የሚታይ ይመስላል - በሰዎች ውስጥ በተቀረጹት መልኮችና ሃሳቦች። እንግዲህ ፣ ይህ በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ከመጀመሪያ ጊዜ ጀምሮ እንደ ዋና ዓይነት መታሰቢያ ብቅ ይላል - እንደ " ጥንታዊ ሃይማኖት ህሊና " …..) ዘመናት በፊት እንኳን። ይህ የህሊና ደረጃ ደግሞ እንዲህ ዓይነት ተቃራኒ ነገሮችን ይይዛል - ሰዎች በህይወታቸው ሲለማመዱ ፣ ከመላ ጎደል " የሚታዩ " ተቃራኒ ነገሮችን ......) ። ቀረብ ብለን ስናይ እግዚአብሄርን በዚህ ዓይነት ማየቱ አስቸጋሪ ገለጻ ይገልጻል (...)። የፈጠራ ታሪኮች፣ በርግጥ ለልጆች ጠቃሚ ሊሆን ከሚችለው፣ ከዚህ የምልክታዊ ዓለም ጋር ፈጠራ ባለበት ሁኔታ ለመገናኘት ሞክረዋል። ዳሩ ግን ፣ አዋቂዎች ፣ ከነዚህ ምልክቶች አልፈው ሊሄዱ ሊሞክሩ ይችላሉ - በብዙ ሰብአዊ ገጽታዎች የሚገናኙ ምልክቶች። ዳሩ ግን ትክክለኛው ችግር ስለ እግዚአብሄር እነዚህ የውሸት ጽንሰ ሃሳቦች እንዲያቃስቱ ከማድረግ ይልቅ እግዚአብሄርን በቀጥታ መፈለግ ነው።

ይህም አንድ ሰው ይህንን ሁሉ በራሱ ጥረት ይቋቋመዋል ወይም ይችለዋል ማለት አይደለም። ይህንን ሁሉ በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሱስ ትክክለኛውን መንገድ፣ኃይል ወይም ምህረት ያቀርባል። እውነትን የሚፈልጉ ክርስቲያኖች፣ ክርስቲያን ባለ ታሪኮችና ክርስቲያን ቀማሚዎች ወደ በለጠ (ፍፅምና) አቅንተዋል (5፡ 48፤ ዮሐንስ፤ 10፡ 34ን ያወዳድሩ) ። ሌሎች ብዙ ክርስቲያኖች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ተመሳሳይ ልምድ አላቸው። በውስጣቸው ቢፈልጉም፣ በማህበራዊ ሕይወታቸው እምነታችውን ተግባራዊ ቢያደርጉም ወይም እኛ "ሙሉ ክርስትና" ብለን እንድምንጠረው ሁለቱንም ቢያጣምሩት ምንም አይደለም። ብዙ ሌላ ባህሎችም ለዛኛው ውስጣዊ ግጭቶች መፍትሄ ለማግኘት ሽተዋል፤ ለምሣሌ ያህል የታኦእስቶች ቀማሚዎችና አንዳንድ የዮጋ ትምህርት ቤቶች 3)

3) ዮጋ የሚለው የሕንድ ቃል፣ ቃል በቃል ሲተረጎም "በቀምበር አጥምደው" ማለት ከሥር ከመሰረትና ከዘላለማዊነት ጋር እንደገና ለመገናኘት መፈለግ ማለት ነው።

"እግዚአብሔር- ሰው" የሱስ ክርስቶስ፣ ‘አዲሱ አዳም’ ሰብአዊ ዘሮች ከዛ ጊዜ ጀምሮ የተሸፈነውን የቀድሞ በህርያቸውን መልሶ ማግኘት የሚችሉ ለመሆናቸው ምልክት ነው። በአሁኑ ሰዓት አደገኛ የሆኑትንና፣ የተሳሳቱትን በህርያትን ለማስተካካል ጊዜው ነው። የሱስ፣ ለምድር እንደ "ዕድለኛ እጣ"፣ ለሕይወት ትርጉም ቀዳሚው ምንጭ መገናኛ የሆነውን እግዚአብሔርንና በከፍተኛ ደረጃ ያደገውን የስው ንቃተ ኅሊና ወክሎአል። የመበስበስ ኃይሎችንም ተቋቋሞአል። ከሰዎች የተለየ ቢሆንም ቅሉ ደግሞ በተለይም ሰዎች ይህንን አውቀው ቢያደርጉ ማድረግ እንድችሉ ዘንድ የገለጠ ሰብእዊ ፍጡር ነው። ዳሩ ግን ስለ ታሪካዊዉ የሱስ ለማያዉቁት እንኳን ትንሳኤዉንም ጨምሮ ሕይወቱ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል። ይህም በሼልድሬክ ምርምር እንደተገኘው፣ አንድ ዓይነት እንስሳት በደሴታቸው ውስጥ በጋራ በሆነ የኃይል መስክ ተፅዕኖ ሳቢያ አንድ ዓይነት ነገር ከተማሩ በኋላ በሌላ ደሴቶች ውስጥ የሚገኙ እንደዚያው ዓይነት እንስሳት አንድ ነገር በፍጥነት ለመማር እንደሚችሉ ዓይነት ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ ያለ ቤተክርስቲያን ከእግዚአብሔርና ከክርስቶስ ጋር ግንኙነት ሊኖር ይችላል፤ ዳሩ ግን፣ ተገቢ የሆነ የክርስቲያኖች ማህበረሰብ ጠቃሚ ነው። ተጻራሪ የስነ መለኮት ትምህርቶች ክርስቶስን እንደ መንፈሳዊ አማካሪ ወይም የማህበረሰብ ለውጥ አቅንቃኝ ብቻ አድርገው የሚያቅርቡበት ሁኔታዎች ከእንግዲህ ወዲህ የመጨረሻ አማራጭ ሊሆኑ አይችሉም። ዳሩ ግን፣ በተላይም አንዱ ከሌላው በተሻለ ሁኔታ የሚያውቅ ከሆነ ለአንድ ሰው ፍንጭ ይሰጣል። እያንዳንዱ ግለሰብ በግል ክፍሉ ሆኖ እራሱን ለክርስቶስ አስተካክሎ መስጠት ይችላል። ዳሩ ግን በመጨረሻ ደግሞ በገበያ ቦታ ሊሆንም ይችላል። ለዚህ ዓላማ አንድ ሰው በወንጌሎች የቀረቡትን የራሱን ባህርያት ማስታወስ ይችላል። ክርስቶስ ከሞት ተርፎ በትንሳኤ ድል እንዳገኘ የሚይይ ሰው ክርስቶስ በአሁኑ ሰዓት እየሠራ እያለ ሊገናኛው ይችላል።(ዘውትር ከክርስቶስ ውጭ ባሉበት ሁኔታ ሰዎች ከሞት ተርፈው የሚያቅርቡት ብዙ ምስክርናቶችም አሉ)። አንድ ሰው ሁሉን ነገር እንደሚይዝለት፣ ከራሱ ጋራ ለእግዚአብሔር እንደታላቅ ወንድም "በርሱ ስም" የጸሎት ስሜት ሊሰማው ይችላል (ለምሳሌ፣ ዮሐንስ 15፡16፤ ማቴዎስ 6፡ 7-15፤ ማቴዎስ 6፡ 18፡ 19-20)ን ይመልከቱ።

እግዚአብሔር፣ መሠረቴ፣ ረድኤቴና ተስፋዬ!
ከየሱስ ክርስቶስ ጋር በአንድነት ከአንተ ዘንድ ለምመጣልኝ ለሁሉም ነገር ይድረስህ ምሥጋናዬ**፤ እኔና ከአንተ አርቆኝ ለወሰደኝ ለሁሉም ነገር ይቅር እንድትለኝ እለምንሃለሁ፤ በዚህ በዝምታ፣ እባክህን በመንፈስህ ጠቢብ አድርገኝ***፤ በመንገዴ አንተ ሳበኝ

*) ማርያምን የማጠቃለል አዝማሚያ ያለው ሰው ይህንን ማድረግ ይችላል። በዚህ መንገድ የወንድና የሴት ባህርያት ደግሞ ጎልተው ይታያሉ።
**)
ተጨማሪ ልምምድ መሆን የምችለው ደግሞ፡ በመጀመርያ እንደ ጭንቀት፣ ጥላቻ፣ ቁጣ፣ ግድየለሽነት፣ ከልክ ያለፈ ድፍረት፣ እጅግ በጣም ከባድ የሆነ ጥርጣሬን ወይም ችግሮችን የመሳሰሉትን አሉታዊ ስሜቶችን መመልከት ያስፈልጋል። እነዚህ ነገሮች በቃላት ወይም በአእምሮ ብቻ ሆነው እንደሆነ እንኳን ማቴዎስ 5፡22ን ያማሳክሩ። ሁለተኛ፣ እነዚህን ነገሮች ከማመንዠግ ይልቅ ነገሮቹ ምን እንደሆኑ በደንብ ለማወቅ እንድቻል ዘንድ መጠበቅ ያስፈልጋል። ሦሥተኛ፣ እነዝህን ችግሮች በፀሎት ለእግዚአብሔር አሳልፎ መሰጠት ተገቢ ነው። ከዚያም ባሻገር እንደዚሁም የራስን መላ ሕይወት በእግዚአብሔር ወይም በክርስቶስ እጅ አሳልፎ መስጠት ይቻላል። አራተኛ፣ አንድ ዓይነት እፎይታ እስኪገኝ ድረስ መጠበቅ ያስፈልጋል።
***)
ፀጥታ "በደረሱብን ነገሮች ላይ እንድንረጋጋ"፣ መፍትሄ ለመሻት በተቻለ ሁኔታ እንድንዘጋጅ ወይም በፀሎት ላይ እንድንሆን ያደርገናል። ከዚያም አዲስ ለሚከሰቱብን ነገሮች የበለጠ ክፍት እንድንሆን ያደርገናል።

በዚህ መንገድ ላይ የሥነ ምግባር አስፈላጊነት

በመንገዱ አንድ ደረጃ፣ ከሁሉም በላይ የሆነውን "እግዚአብሔርን መውደድ"ና "ባልንጀራህን እንደ ራስህ መውደድ" (ማቴዎስ 19፡19) ነው። አንድን ሰው መውደድ ደግሞ አንዱ ለሌሎች ለሚያደርገው ተግባር የመፈለጊያ ጥረት አካል ሊሆን ይችላል። የራሱ ባህርይ በመሆኑ፣ፍቅር ከጥበብ ጋር በመቀላቀል ሰውን ከክርስቶስ ጋር ሊያገናኝ ይችላል። የመልካም ተግባሮች መንገድ ደግሞ ከሚያመጣቸው ለውጦች ጋር የክርስቲያንን መንገድ ግልጽ ያደርገዋል። የሱስ የቀድሞውን የመልካም ሥነ ምግባር መሠረተ ሀሳቦችን ጠብቆአል፤ ምክንያቱም፣"ሰው [ዘውትር] የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና"( ገላትያ 6፡7)፤ ዳሩ ግን፣ እርሱ ከውጫዊው ህግ ይልቅ በግለሰብ ኃላፊነት ላይ አትክሮአል። በውስጣችን አንድ ነገር እንዳለ አንድ ሰው ሊያስተውል ይችላል፤ ለምሳሌ፣ ክርስቶስ በራሱ ሕይወት ምሳሌ ሆኖ እንዳሳየው፣ ከመንፈሱ ጋር ተስማሚ በሚሆን መንገድ ክፋት ወይም ደግነት መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል። ይህ ነገር በአንድ ግለሰብ ልብ፣ ነፍስ ወይም መንፈስ ውስጥ ይንፀባረቃል። በተቻለ መጠን፣ ዘወትር የክርስቶስን የታወቁትን ባህርያት የራስ ባህርይ ማድረግ ጠቃሚ ነው። ለጊዜው ትላልቅ ለውጦች ባይከሰቱም ቅሉ፣ ከርሱ ጋር የጠበቀ ግኑኝነት ይፈጠራል።

በዚህ ሁኔታ በምህረት የሚመነጨው ኃይል፣ እንደገና ከ"ውጫዊው" ክርስቶስና እግዚአብሔር የሚቀርበውን ሁለንተናዊውን የማዳን ኃይል ይስባል። እዚህ ላይ ደግሞ የያንዳንዱ ሰው የመለማመጃው መንገድ የተለያየ ሊሆን ይችላል። ዳሩ ግን፣ በዚህ ሁኔታ በአንድ ሰው ላይ የሚመጣው ለውጥና ነገሩ የሚከሰትበት ሁኔታ በጥልቀት ሊሆን ይችላል። ጥቂት "ቅዱሳን"ንና "ረቂቅ በሆነ መንገድ ከአምላክ ጋር የሚገናኙ" ሰዎች ከዚህ ቀደም የቀሰሙአቸው ልምዶች በኛው በ"ጥፋት " ዘመን በተራ ሰዎች አማካይነት ይሰራጫል። አንድ ሰው ጠቃሜታውን ወዲያውኑ ሊገነዘበው ስለማይችል፣ ይህ ሃሳብ እዚህ ጋ መጠቀስ አለበት። ነገሩ የሚያሳስባቸው ሰዎች ይህንን ለዋጭ ኃይል መቀበል አለባችው፤ አለበለዚያ እንደ አንድ ዓይነት "ፍርድ" እንዲሰማቸው ከርሱ ጋር ተስማሚ የሆኑትን ባህርያት ያላጎለበቱትን ሰዎች መሰናክሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ይመታል።

ወደ አንተ የሚሄዱትን፣ ሌሎችን እንዳላሰናክል አንተ ምራኝ፤ እንደ ፈቃድህ ሌሎችን እንድረዳ ዘንድ አንተ ምራኝ በመንገዴ አንተ አድነኝ* በፍቕርህ እንድጓዝ እርደኝ

*) እዚህ ጋ ሌሎችም አባባሎች ሊጨመሩ ይችላሉ።

ከጥንት፣ታሪክ ካልተጻፈበት ዘመን ጀምሮ በባህሎች ውስጥ ያለው ሰፊው ተመሳሳይ የዕድገት ደረጃ

ከልጅነት እስከ ጎልማሳነት እንዳለው የዕድገት ደረጃ፣ እንዲሁም የሰው ባህሎች በተለያየ የንቃተ ህሊና ደረጃዎች አልፈዋል። በአንዱ በኩል አዳዲስ ችሎታዎች (ፈቃድ፣ ከድሮ ይልቅ በአሁኑ ዘመን ሰው ሃሳቦቹንና ስሜቶቹን የመግለጽ የበለጠ ነጻነት አላው) ሲከሰቱ በሌለው በኩል ደግሞ በችግር ውስጥ በሚከት ሁኔታ ከመለው "ተፈጥሮ" ጋር ያለው ቅርበት ዋጋ አጥቶአል (ለምሣሌ፤ ጂን ገብሰር፣ በጀርመንኛ " ኡርስፕራንግ ኣንድ ገገንዋርት"፤ "አሮጌ"፣ "ጠንቋይ"፣ "ረቂቅ"፣ ምሁር ንቃተ ህሊና እያሉ የማመዛዘን አመለካከት አለ። ከዚያ ባሻገር የተሻላና የተቀናጀ ግምታው ሃሳብ ሊመነጭ ይችላል። ተዋቂ ሰዎች እንደዚሁ እያደጉ የሚሄዱት ደረጃዎች ለባህሎቻቸው ፍሬያማ እንዲሆኑ ረድቶአቸዋል። ይህ የሆነውም ብዙ መሰናክሎችን አልፎ፣ ዳሩ ግን በፊት እንደተጠቀሰው የከረሙትን ችሎታዎች አክስሞ ነው። በአሁኑ ታሪክ፣ ስዎች ለመኖር ከፈለጉ ትንሽ ሆነ ትልቅ አዝጋሚ ለውጦችን የበለጠውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የተደቀነባቸውን ፈተና መጋፈጥ አለባቸው4) ። ከእ ኤ አ 2000 ዓ ም አካባቢ ጀምሮ ይህ የሚቻል ነገር ነው። ይህ ዕድገት እንደ አእምሮ ያሉትን የቀድሞ ወይም አሮጌ ባህርያትን ማበላሸት ወይም መቀነስ አይገበውም። በቂ ግለሰቦች የበለጠውን ምሉዕ የሆነ የተለምዶ አስተሳሰብ ቢያጎለብቱና፣ ከመለኮታው ሥር መሠረታቸው1) ጋር ያለውን ግኙኝነታቸውን ቢያሳድሱ፣ ሰብአዊ ፍጡር "ከላይ" ዕርዳታ በማግኘት በ"መጨረሻው ዘመን" ከሚመጠው ጥፋት ጋር ያለውን ውድድር ሊያሸንፍ ይችላል። ይህ ደግሞ በዓለም ላይ እንደ ሰላም እንቅስቅሴ ከመሳሰሉት ጋር ግኑኝነት አለው፤ ሁሉም በጎ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች የግድ በ"ጨዋታው" ላይ ሚና አላቸው። በርካታ ሰዎች በቀጥታ ተቋቁመው ባሉት የሃይማኖት ትምህርት ቤቶች መስመር ይህንን በግልጽ እየፈለጉት ነው። አንዳንድ "መሃል ሰፋርነት" ሊኖር የሚችል ቢሆንም ቅሉ፣ ያለፈውን ነገር በማስረሳት እገዛ እያደረጉ ወደፊት ይገሰግሳሉ። አንድ ሰው ምንም ያስብ ምንም፣ ዓላማው የሰውን ዘር "ማዳን" ወይም በንቃተ ህሊና መሻሽል ነው። የቀድሞ "መርሃ ግብር" ወዴት እንደሚመራ በግልጽ የሚታወቅ በመሆኑ ዘመናዊ የስነ ምግባር ደረጃዎች መለወጥ አለባቸው። ማንኛውም ነገር የሙሉ ነገር አካል ነው፤ እንዲሁም ሁሉም በጎ ነገሮች ዓለምን ይጠቅማሉ።

በሄርበርት ግሩህል በመጨራሻው መጽሐፉ ውስጥ በጀርመንኛ አባበል፣ "Himmelfahrt ins Nichts" ፣ (ትርጉሙም ወደ ባዶ ሥፍራ ማርጋት)፣ አንድ ሰው የተረሳው የኃይልና የዕድገት ምንጭ ይኻውም ዕድል ብቻ (እግዚአብሔርን ለማለት ነው) በሀሳቡ ይመጣበታል እንደሚለው፣4) እኛ በተስፋ አስቆራጭነት አመለካከት አንስማማም፤

ሰዎች ሞትንና ሕይወትን የተመለከቱበትን ዉሳኔዎች በአንተ እጅ ይጥሉ ዘንድ በመንፈስህ አነሳሳቸው* ለተፈጥሮህ የሚሠሩትንም እርዳቸው*** ይህን ዓለም ተስፋ ወደሰጠሃው ወደ አዲሱ ዘመን ዘልቆ ይገባ ዘንድ ምራው**

*) እዚህ ጋ ዝርዝሮችም ሊጨመሩ ይችላሉ፤ ወይም ‘ሁከትን መካብ ማቆም’፣ ችግሮችን በማቃለል አንድ የሁከት መንስኤ ማስወገድ’፤ ሰላማዊ ሰዎች ሰብአዊ መብታቸው ተከብሮ ለመኖር የሚያስችላቸውን የደህንነት እርምጃችን ብቻ ተግባራዊ ማድረግ’ ’ታዋቂ ከሆኑ ከተለያዩ የሃይማኖት ሰዎች ጋር ውይይት ለመጀመር፣ ከመሳሰለው ፀሎት በኋላ በአማላጅነት ሊገባ ይችላል…. **) ሉቃስ 11፡2፤ 21፡31። ራዕይ 11፡ 6፤… እግዚአብሔር ለርሱ የተሰጠውን ፍቅር ያከፋፍላል።

በትንሹ ሆነ በሰፊው ወደ እግዚአብሔር "መመለሻው" ቅርብ ነው።

ዮሐንስ 1612-13: " 12. የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። 13. ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።"

 


መረጃ፦ የሱስና እስልምና

በተለያዩ የሃይማኖት ድርጅቶች መካከል ያለው ውይይት.
ይህ ገጽ - ለብዙ ዓመታት እየተደረገ እንዳለ በተሻለ ሁኔታ ለመረዳትና በሃይማኖቶች መካከል ላላው ውይይት አስተዋፅዖ ነው። ይህ ገለጻ መለውን እስላም በተወሰነ ፈርጅ ለመመደብ አይሞክርም። በእስልምናም ቢሆን የተለያዩ አመለካከቶች አሉ. 

ቁርአንና ሌሎች "የመጻሐፍቱ ሃይማኖቶች"

እስልምና ማለት "ለእግዚአብሔር ፈቃድ እራስን አሳልፎ መስጠት" ማለት ነው።

የእስልምና ቅዱስ መጽሐፍ፣ ቁራን (ቁርዓን) በክርስትናም፣ ሊቀ መልአኩ ገብርኤል መሆኑ ተለይቶ በሚታወቀው በጅብሪል አማካይነት፣ ለነብዩ መሐመድ (ሙሐመድ) የተላለፈ መለኮታዊ ሀሳብ እንደሆነ ይታመናል። በእርግጥ ቅዱስ ቁርአን ከእስልምና መጻሕፍት ሁሉ የበለጠ ጠቃሚ መጽሐፍ ተደርጎ መወሰድ አለበት። ተጨማሪ ወጎች ("ሱና"፣ በተለምዶ፡ "ልምድ) ከነብያት አባበሎች ጋር ቁርአንን ለመተርጎም አንድ ሚና አላቸው። ነቢይም ቢሆን፣ በግል ባህርይው፣ ሰው እንጂ አግዚአብሔር አይደለም። በርካታ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱሳቸውን በደንብ እንደማያውቁት ሁሉ ቅዱሳት መጽሐፍቶቻቸውን የማያውቁ እስላሞች እንዳሉ ደግሞ መገንዘብ ይገባል።

ቅዱስ ቁርአን ክርስቲያኖችንና አይሁዶችን አንዳንድ ጊዜ በቀጥታ "እናንተ የቅዱሳት መጻሕፍት ሰዎች" (ለምሣሌ ሱራ 4፡171) እናም "እናንተ የእሥራኤል ልጆች" ብሎ ይጠራቸዋል። ሆኖም ግን አብዛኛዎቹ ለዚህ ጉዳይ ቦታ ባይሰጡትም ቅሉ፣ ስለዚህ እነርሱ በዚህ ቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በተጻፈው ነገር ፍላጎት ሊኖርባቸው ይችላል። ቢሆንም ቅሉ የሃይማኖት ሳይንስ ሁሉንም ሃይማኖቶች ያጠናል- ከሁሉም ነገሮች መካከል፣ የአተረጓገማቸውን ታሪካዊ ዕድገት ያጠናል። ዳሩ ግን፣ ቅዱሳት መጻሕፍት በአክብሮት መጠናት አለባቸው። ከቁርአን ተቺዎች አንዱ ክፍል እንዲሁ ብሎን ጽፎአል፦ ዋና ቁርአን በእግዚአብሔር በጥሩ ቦታ ተቀምጦአል- ለንጹህ መላዕክት ንጹህ ነቢያት ብቻ ይቀርቡታል፤ ከነርሱ ሌላ ክፍል እንደዚህ ብሎ ይተረጎማል፣ በምድር የቁርአን አንባቢ ንጹህ መሆን አለበት።

ነብዩ፣ ነብያት በሚፈለጉበት ጊዜ፣ ለጊዜው (ወይም በመካከል ላለው ጊዜ) የተላከ እንደሆነ ተደርጎ ይታያል (ሱራ 5፡19*)። ቅዱስ ቁራን በነብዩ መሐመድ ትምህርቶች "አማኞች"ን፣ የቅዱሳት መጽሐፍት ሰዎችን" ና "አማኞች" ያልሆኑትን ለይቶ ያስቀምጣል። የ "ቅዱሳት መጽሐፍት ሰዎችን" ከ እስላሞች ሌላ በአንድ ወጎች ላይ የተመሠረቱትን በተለይም አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን እንዲሁም አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ዞሮአስትሮችን ወይም ፓርስዎችን ያጠቃልላል (ፓርሲስ፤ ሱራ 22፡17*)። ቁራን ስለ አንድ እግዚአብሔር፣ ከዚህ በኋላ ላለው ስለ መጨራሻው ፍርድ፣ ስለሕዝቦቻቸው ወይም ስለዘመናቸው ፀሎት የሚያደርጉትን በሁሉም የደረጃ ተዋረድ ያሉትን ነብያት ይቀበላል (ለምሣሌ፤ ሱራ 6 ፤ 83-92፤ሱራ 7፤ሱራ 4፤ 136*)። የነዚህ ሃይማኖት ሰዎች በጋራ መሠረተ ሐሰቦች እስካመኑ ድረስ፣ ቁራን እራሱ አማኞች ያልሆኑ ብሎ አይጠራቸውም (ለምሳሌ ሱራ 5፡48*)። በእስልምና የመጀመሪያ ምዕተ ዓመታት ክርስቲያኖችና አይሁዶች ወደ እስልምና እንዲመለሱ አልተገደዱም- በቁርአን ትምህርት መሠረት ፣ " በሃይማኖት ግዳጅ የለም"፣ ሱራ 2፣256። 
አብርሃም በአንድ እግዚአብሔር ማመንን ከመሰረቱ ፣ ለምሳሌ እንደ አንዳንድ መናኞች ከ"ሐኒፎች" እንደ አንዱ ይታያል።
"አላህ" ከቅድመ እስልምና አረብኛ "አል እላህ"- እንደ ሴማውያን ቃል ሆኖ፣ ከመለ ጎደል በእርግጥ ከሆነው በሙሴ መጻሐፍት የእግዚአብሔር መጠሪያ ስሞች አንዱ ከሆነው በዕብራይስጥ ኤሎሄም ጋር አንድ ዓይነት መነሻ አለው።

"አማኝ ያልሆኑት " - በአጠቃላይ፡ "ሸፋኝ" - በትክክለኛ ስሜት ብዙ አማልክት አምላኪዎች - መሐመድ በአረቢያ እንደተዋጋና መጽሐፍ ቅዱስ ለክርስቲያኖችና ለአይሁዶች ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው፣ ጣዖት አምላክዎች ናቸው። ዛሬ በሰፊው በአንድ እግዚአብሔርና በመጨራሻ ፍርድ የማያምኑትንና እስልምና አማኞች እንዳልሆኑ ያያቸዋል። አንዳንድ ጊዜ ቃሉ ሁሉንም እስላም ያልሆኑትን በውሸት ያጠቃልላል፤ አንዳንድ ጊዜ እራሳቸው እስላም ሆነው ልዩ አመለካከት ያላቸውንም ያጠቃልላል።

የሱስ ክርስቶስ በቁርአን

እዚህ ጋ መገንዘብ ያለብን ነገር፣ ቁርአን የሱስን እንደ ነብይ፣ ከእግዚአብሔር የተላከ ነብይ፣ ያለምንም ትርጉም የእግዚአብሔር "ቃል"፣ እናም እንደ "እግዚአብሔር መንፈስ"፣ (ሱራ 4፣171*፣ "እንደ አዳም የተፈጠረ" (ሱራ 2፣ 3 ፣ 5*….) አድርጎ ይቀበለዋል። ይህም አንዳንድ ዘመናዊ የክርስትና ሥነ መለኮት ሊቃውንት የሱስን የማህበራዊ ለውጥ አምጭ ብቻ አድርገው ከሚቀበሉት በላይ ነው። ክርስቲያኖች በመሐመድ ጊዜ ይህንን በአካል ገምተውታል (የሱስ እንደ እግዚአብሔር ልጅ ብቻ ነበር የሚታየው)። በኋላ የመጣው የሦሥቱ ሥላሴ ህገ ፅንሰ ሀሳብ በቁራን ተቀባይነት አላገኘም። ከአንድ ጋ መጥቶ መረጃ የሚፈልግ ሰው ሊረዳው እንደሚችል እንደ "እግዚአብሔር ቃል" (ዮሐንስ 1) አድርጎ በእውነት የሚያስረዳ ሰው በዛ ዘመን በቀላሉ አይገኝም ነበር (ለምሣሌ፤ ሱራ 6፣ 101)።
በሮሜ 1፡4፣ የሱስ በራሱ መንፈሳዊ ኃይል እንደ "ልጅ" ተተከለ ይላል- እናም እንግዲህ አልተወለደም።
እግዚአብሔር አይወለድም፤ የሱስን ፈጠረው እንጂ "አልወለደውም" ከሚለው ከእስልምና እምነት ጋር ክርስቲያኖች ሊስማሙበት ይችሉ ይሆናል። በተጨማሪም በግሪክ ቃል "ሎጎስ" የሚባለው የሱስ ለመለኮታዊ መነሻነቱ ወይም የየሱስ ክርስቶስን ተልዕኮን ለማመልከት የሚጠቀሙበት ቃል ነው። ይህም በቁርአን የሱስ የተባለው በወንጌል "ቃል" ተብሎ ነው የተተረጎመው። የቁርአን ጽሑፎች በሙስሊሞች ወይም በክርስቲያኖች ገና ሙሉ በሙሉ ያልተስተዋሉትንና በቃላት ምክንያት ጥቅም የሌለውን ጥላቻ የሚያስከትሉቱን ሚስጥሮች ይዘዋልን? አንዳንድ ከአንድ በላይ አምላክ መኖሩን እንደሚያሚኑት ሰዎች፣ መረዳት እንደምገባን ደግሞም ክርስቲያኖች ይህንን ትምህርት በቃላት ሲናገሩ እንደ የሱስ ትምህርት አይደለም የሚያስተምሩት። "ወደ (እግዚአብሔር) በእኔ ስም ፀልዩ ። ይህም ማለት ከየሱስ ትምህርት ጋር ስናስተያየው ነው ( ዮሐንስ 15፡16)። በየሱስ ሕይወት የሱስ ራሱ ሰዎችን ሊመራቸው በሚችለው በአንድ እግዚአብሔር ዙሪያ ነው የሚሽከረከሩት።

ሎጎስ (በበግሪክ፣ በዮሐንስ ወንጌል፣ እዚህ ጋ ከክርስቶስ ጋር የተያየዘው፣ "የእግዚአብሔር ቃል") በፓሬት የጀርመን ትርጉም፣ ከየሱስ ተለይቶ ነው የተቀመጠው። ሌሎች የቁርአን እትሞች እንደ እግዚአብሔር "ጉዳይ" ወይም እንደ እግዚአብሔር "ትዕዛዝ" አድርገው ያስተውሉታል (ሱራ 13፤12፤ ሱራ 11*)።

ቁርአን የሱስን "እንደ አዳም" ከአፈር የተፈጠረ አድርጎ ይመለከተዋል (ሱራ 3፡ 59*)፤ እናም የሱስ እንዲወለድ ዘንድ ከእግዚአብሔር መንፈስ ዘንድ መልዕከተኛ መላኩን ይናገራል (ሱራ 19፣17-22*)። የክርስቲያኑም በኩል መልአኩ ለድንግል ማርያም የሱስ ከመንፈሰ ቅዱስ እንዲወለድ ዘንድ ከእግዚአብሔር መንፈስ መላኩን ይናገራል። በተጨማሪም፣ የሱስ በመንፈስ ቅዱስ/ በቅድስና መንፈስ ብርታት እንዳገኘ ይገልጻል (ሱራ 5፣110*)። የየሱስን ሕይወት በተመለከተ መንፈስ ቅዱስም ተጠቅሶአል (ሱራ 5፡110)። 

እንደ ቁርአን አባባል ወጣቱ የሱስ ትንሣኤውን አብስሮአል (ሱራ 19፡ 33*)። ዳሩ ግን እዚህ ጋ፣ በቁርአን ዘወትር እንደተጠቀሰው በፍርድ ቀን ስለሚሆነው ስለ አማኞች ትንሣኤ ሊሆን ይችላል (ከዚህ በታች ሱራ 4፡159 የተጠቀሰውን ይመልከቱ)። ቁርአን የሱስ ሳይሞት ወደ ሰማይ በእግዚአብሔር ተወሰደ ይላል (ሱራ 4፡ 157-፤ሱራ 3 ፡ 55*)። 
የሱስ ወደ ሰማይ ከማርጋቱ በፊት መሰቀሉን፣ መሞቱንና ሞትን ድል መንሳቱን በተመለከተ ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች አይስማሙበትም። ሙስሊሞች እንደሚያምኑበት ክርስቲያኖችም የሱስን እግዚአብሔር ሳይሞት ወደ ሰማይ ወሰደው ይላሉ። ዳሩ ግን፣ ሁለቱም የሱስ "እንዳልሞተ" ያምናሉ። ለምሣሌ ከሞት በተነሳ ጊዜ ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ መናገሩን መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል።
በሱራ 3፡55ና 5፡ 48* "ንፁህ አደርገዋለሁ ተብሎአል" እናም "…አንተ ወደኔ ተመልሰህ ትመጣላህ፤ እኔ(እግዚአብሔር) አንተ ስላልተስማማህበት ጉዳይ ውሳኔ እሰጣለሁኝ" ብሎ ይናገራል። ስለዚህም ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች ከመጣላት ይልቅ ለቀሩት ሚስጥሮች መፍትሄ ለማግኘት መጠበቅ ይኖርባቸው ይሆናል።

ቁርአን ደግሞ የመጨረሻ ፍርድንና የአማኞችን ትንሣኤ ይይዛል (ለምሣሌ ሱራ 36፣77-83፤ ሱራ 69፣13-37፤ ሱራ 75፣99*) የሱስ እንደገና ተመልሶ ይመጣል፣ ለቅዱሳን መጻሕፍት አማኝ ለሆኑ ሰዎች ምስክር ወይም ዳኛ ይሆናል (ሱራ 4፣159፤ ሱራ 16፣89 * ( የሰው ክብር)። እነዚያ - ደግሞ እስላሞች ያልሆኑም-፣ በእግዚአብሔርና በመጨራሻ ፍርድ እንዳለ የሚያምኑና መልካም ሥራ የሚሠሩ ፍርድን መፍራት የለባቸውም (ሱራ 2 ፡ 62፤ሱራ 4፣123-124፤ ከሱራ 7፣170* ጋር ያማሳክሩ)። በቁርአንና በመጽሐፍ ቅዱስም መሠረት፣ ክርስቲያን፣ እስላም ወይም አይሁድም ቢሆኑ፣የመጨራሻ ፍርድ የእግዚአብሔር እንጂ የሰው ሥራ አይደለም። 
( እንደዚያ ዓይነት በሐይማኖት መካከል በሚደረገው ንፅፅር ቁርአን ገለልተኛ ስለመሆኑ ጥርጥር የለውም።)

የሥነ ምግባር መሠረታዊ መርሆዎች

የእነዚህ የሦስቱ የታወቁ የ"አብርሃማዊ ሃይማኖቶች" የሥነ ምግባር መሠረታዊ መርሆዎች* አንዱ ከሌለው ጋር የተያያዙ ናቸው። ትዕዛዛቱ በቁርአንም አሉ፣ ዳሩ ግን በተመሳሳይ መንገድ አልተዘረዘሩም(ለምሣሌ ሱራ 17፣22-39፤ ሱራ 5፣38-40፤ ሱራ 2፣188፤ ሱራ 4፣135፣ ሱራ 2፣195፣ ሱራ 17፣70 *)። ቁርአን ለምሣሌ ማንኛውንም ሰላማዊ ሰው መግደል ሀገወጥ ነው ይላል( ሱራ 5፣27-32*)። ጃሃድ (ግሃድ) ማለት፣ መዋጋት፣ መታገል፣ "የቅዱስ ጦርነት" ትርጉም የተወሰደው ከቁራን ሳይሆን ከመሐመድ አባባሎችና ከእስልምና ህግ ትምህርት ቤቶች ነው***። በውስጥ ሰውነት ወይም በአእምሮና በግብረ ገብነት ከራስ አመጽ ጋር መዋጋት በውጭ ካሉት ከሁሉም ግጭቶች የሚበልጥ "ታላቅ ጂሃድ" ነው ይባላል። መጀመሪያ " በዓይንህ ውስጥ ያለውን ምሶሶ አውጣ" የሚለውን የክርስቶስን አባባል ከዚህ ጋር አወዳድር። በዚህ መንገድ ብዙዎች የውጭ ግጭቶች መሠረታቸው ይላላል። የ "ቃል ጂሃድ" በሰላም ስለአንድ ሰው እምነት መናገር ነው። "የእጅ ጂሃድ" ተንቀሳቃሽ ፣ የአማኙ የማስተማሪያ ምሣሌ ነው። የሰይፍ ጂሃድ" ደግሞም " ትንሹ ጂሃድ" የሚባለው የሚፈቀደው የተጠቃ አማኝን ለመከላከል ብቻ ነው (በቁራን ሱራ 2 ፡ 190* ላይ ካለው ጋር ያገናዝቡ)። ዳሩ ግን ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር በመገናኛት ስለሚከሰተው "ኃይለኛነት" በቁራን ውስጥ ሊገኝ ይችላል (ሱራ 48 ፡ 29 ፤ ሱራ 47፡4*)። ለምሣሌ ያህል ሞስሊም ካልሆነ ሰው ጋር ለመጋባት መከልከልን ጨምሮ የጾታዎችን ግኑኝነት በተመለከተ ሰፋ ያሉ ባህላዊ ህጎች አሉ።

የእስልምና ልምምድ፤ ከእግዚአብሔር ወይም ከአላህ ሌላ እግዚአብሔር የለም እናም መሐመድ የእግዚአብሔር ነብይ ነው፤ የዕለት ተዕለት ፀሎት ይደረጋል ( ሱራ 2፣177*)፤ ዓመታዊ የጾም ወር ወይም ራመዳን ይጠበቃል( ሱራ 2፣ 185*)፤ ቢያንስ በዕድሜ ዘመን አንድ ጊዜ መንፈሳዊ ጉዞ ይደረጋል ( ሱራ 2፣ 196*)እናም "ዘቃት" ወይም የሃይማኖት ሥጦታ ይሰጣል( ሱራ 2፣177*) የሚሉትን ተግባሮች ያጠቃልላል።

በዛሬው እስልምና፣ የሃይማኖት- ስነ ምግባር ጥያቄዎችን የሚወስን ማዕከላዊ ባለሥልጣን የለም። ዳሩ ግን፣ ግልጽ በሆኑ በተከበሩ ምሁራን(ኡላማ) የሚከፈል አቋም በትልቁ ተቀባይነት ያገኛል።

*) ለዚህ ጽሑፍ የጀርመንን ቁርአን - የሩዲ ፓሬትን ትርጉም ተጠቅመናል። በአብዛኛው ጥቅም ላይ የሚውለውን የግብጻውያንንም ቀመር ተጠቅመናል። ሌሎች ትርጉሞች ቁጥሮቹን በተለየ መንገድ ሊቆጥሩ ይችላሉ፤ ከዚያም በዚያው ሱራ ውስጥ የተጠቀሰውን ይዘት ከቁጥሩ በፊት ወይም በፊት ያገኙታል። የቁርአን ምንባቦች ትርጉም ከጀርመን ቁርአንና፣ ትርጉሙ በእስላሞችም ዘንድ ደግሞ ተቀባይነት ካገኘው ከአዴል ቴኦዶር ኮመንተሪ ድጋፍ ተመሳክሮአል (ለምሳሌ በዚያን ጊዜ ዶ/ር እናሙላሂ ከሃን የመለው ዓለም የእስልምና ማህበር ጠቅላይ ጸሐፊ ነበሩ)። የርሳቸው ሀተታ ለእስልምና ት/ቤቶች ባህላዊ አተረጓጎሞች ልዩ ትኩረት ይስጣል። በትክክል ሊረዱት ለሚችሉት ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች፣ አሮጌውን የአረብኛ የቁርአን ቋንቋ መተርጎም በጭራሽ አስቸጋሪ ነው የሚለው አግባብነት የለውም።

***) የመካከለኛ ዘመን "የመስቀል ጦርነቶችም የሰው ተግባር እንጂ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረቱ አልነበሩም( ለምሣሌ የመስቀል ጦርነቶች በአብዛኛዎቹ በዛሬው የአውሮጳ ክርስቲያኖች ዘንድ መጥፎ ዝና ያለው)።

 ወደ ዋናው ገፅ ምረኝ

ወደ ways-of-christ.net/am ዋና ገጽ:

ዋናው ጽሑፍ ከተጨማሪ ዐርዕስቶች ጋር (በእንግሊዝኛ):

የየሱስ ክርስቶስ መንገድ፣ እርሱም ለሰብአዊ ፍጡር ልቦና፣ የሰውን ዘርና ምድሪቱን ለመለወጥ የሚያደርጋቸው አስተዋፅዖዎች፤ በበርካታ ምርምርና ልምድ ላይ የተመሠረቱ አዳዲስ አመለካከቶችን በማፍለቅ የግል ባህርይን ዕድገት ለማጎልበት ተግባራዊ የሆነ ጥቆማን የሚሰጥ ገለልተኛ የሆነ የመረጃ ምንጭ ነው።

"የክርስቶስ መንገድ" ድረ ገፅ የምርምርና የጥናት ፕሮጀክት ነው። "የክርስቶስ መንገድ" በሃይማኖቶች መካከል ሰላማዊ ግኑኝነቶችና ጥልቅ መግባባት እንዲኖር ድጋፍ ይሰጣል። "የክርስቶስ መንገድ" ከቤተ ክርስቲያናትና ከሌሎች ድርጅቶች ገለልተኛ ሆኖ ትርፍ ወይም የፖለቲካ ሥልጣን ለማግኘት ጥረት አያደርግም። "የክርስቶስ መንገድ" የሃይማኖት ስብከት እያደረገ ወይም አባላትን ለመሰብሰብ ዘመቻ እያካሄደ አይደለም ያለው።

 

Imprint:  የባለቤትነት መብት፡

እርስዎ ይዘቱን ሳይቀይሩ ከዚህ ሞገደ ማዕከል ላይ የራስዎን ቅጂ ማባዛትና ለሌላው ሰው መስጠት ይችላሉ።

የተባዘው እ. ኤ. አ በ 1991-2014 ነው፤ በእንቴርኔት መጀመሪያ የታተመው በታህሳስ 31 ቀን 2001 ዓ ም ነው። ይህ እ. ኤ. አ ጥቅምት 4 ቀን 2010 በኋላ የተከለሰው የአማርኛ እትም ነው።

ደራሲ፦ የክርስቶስ መንገዶች ፕሮጄክት (Christuswege / Ways of Christ ™)።

የዚህ የእንቴርኔት እትም አሳታሚ ሄልማት ዛይግሌር።

ይህ " የክርስቶስ መንገዶች" የተባለው ሥፍራ የጥናት- እና ምርምር ፕሮጄክት ነው። " የክርስቶስ መንገዶች" የተባለው ሞገደ ማዕከል The website "Ways of Christ" አጠቃላይ አመለካከት" አለው፣ እናም በሃይማኖቶች መካከል ሰላማዊ ግኑኝነትና ጥልቅ የሆነ መግባባት እንዲኖር ይደግፋል። " የክርስቶስ መንገዶች" ከቤተ ክርስቲያናትና ከሌሎች ድርጅቶች ገለልተኛ ነው - ዳሩ ግን የማንም ቤ/ክርስቲያን ተቃራኒ አይደለም። ቀኖናዊውን ወይም የግትርነት አቀራረብ ሳይቀበል የእምነቱን ቁም ነገር ይጠብቃል። " የክርስቶስ መንገዶች" የሚሲዮናውያንን ሥራ እየሠራ አይደለም ወይም አባላትን አያሰባስብም፣ እናም ትርፍ ለማግኘት ወይም የፖለቲካ ተፅዕኖ ለማድረግ አይቃጣም።

ሥራው የሚያጠቃልለው ሁሉንም የክርስቲያን ዐርዕስቶችንና ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር ያለውን ውይይት ነው። ዋናው መስክ ዘወትር ችላ የተባለውን የክርስቲና መንፈሳዊ ጎን መግለጽ ነው። ዳሩ ግን፣ በዚህ ልዩ በሆነው አመለካከት፣ የክርስቲና ሌላው በኩል - የማህበራዊ ጥያቄዎችን በተመለከተ - በእኩልነት ጠቃሜታ ነው የሚታዩት። ( የዋናውን ጽሑፍ "መግቢያ…"ንም ይመልከቱ።

ከእንግሊዝኛና ከጀርመን ቋንቋዎች ውጭ ያሉ ትርጉሞች ሁል ጊዜ አይታዩም
በአንዳንድ አገሮች ትርጉም ማለት በዚህ ሁኔታ አስተያየት መስጫ ነው ማለት አይደለም።፡

የሌሎችን ሞገደ ማዕከሎች ወይም መጽሐፍት በተመለከተ " የክርስቶስ መንገዶች" በቀጥታ ሁሉንም ይዘታቸውን አይደግፍም።

ለክርስቶስ መንገዶች" ኢ-ሜይል ያድርጉ፡ *) እባክዎን፣ ከተቻለ እንግሊዝኛ ወይም ጀርመን ይጠቀሙ

የዋናው ጽሑፍ እትም የሚገኛው በጀርመንኛ ብቻ ነው - የጀርመንን ዋቢ ይዩ። የዚኛው መጽሔት የማሳተሚያ መብት የሚገኛው በአሳታሚው እጅ ነው፣ ኦ. ቦህም።

Homepage